የግጥም ማእደር

  • ሆድና ህሊና

    ጥንታዊ አባታችን—- ገና አዳም ሳየፈጠር፣
    ይሄ ሁሉ ዘመን —- በሰው ላይ ሰቆጠር፤
    ለምን ይሆን ከቶ —- የሚነሱን ጤና፣
    ሙገት የመገጥሙን —- ሆደና ህሊና።

    የዐለም ፈጥረታቶች —- ገዢ የሆነው ሰው፣
    አስተወሎ መስሪያ —- ህሊና ሲሰጥው፤
    ገና በጅምሩ —- በሆዱ ታለለና፣
    ታናሽ ሆኖ ቀረ —- ተለቁ ህሊና።

    የኽው እስከዛሬ —- ሆድ ባመጣው ጣጣ፣
    ይኖራል የሰው ለጅ —- ከችግር ሳይወጣ፤
    ታላቅ ቡርኩናውን —- ለታናሹ ሸጦ፣
    አስተውይ ህሊና — በሆድ ተለወጦ።

    እርገማን ሆኖብን —- ከአዳም የወረደ፣
    በሰው ዘረያ ላይ —- እሳቱ ነደደ፤
    ዳኛ በሌለብት —- እየተማዋገቱ፣
    ሁድ አና ህሊና —- ስንቱን ሰው አሳቱ።

    የማይቀርው መንገድ —- ያ ጉዞ ሳይመጣ፣
    ከሆ መቆራኘት —- ምን አለብት ብንወጣ፤
    እንደ ብዐሲት ሎጥ —- ድኒ ሳይወርደበን፣
    ለህሊና ኖረን —- ምናለ ብንድን።

     

    ከሰአት ና ዘመን የተወሰደ
    ሻምበል ታደሰ ወ/ገብራኤል

  • ቁርኝት

    የህይወት ጥሪ ነው መሰል፤
    ላንገናኝ ያገናኘን፤
    ላንሰናኝ ያሰናኝን፤
    ላነቆራኝ ያቆራኘን፤
    ባንድ ዘመን ተገናኘን።

    የዘሆን ጆሮን ተመኝሁ፣ ሮርህን ተጠይፌ፤
    በመደቤ ላይ ተቀምጠህ፣ በመርኩዝህ ተደግፌ፤
    የአዞ እንባ ነው አልከኝ፣ የነፍሴን ለቅሶ ከደህ፤
    ከማእድህ ተቓድሼ፣ ብታዛዬ ተጠልለህ።

    የህይውት ጠሪ ነው መሰል፤
    ላንገናኝ ያገናኘን፤
    ላንሰናኝ ያሰናኝን፤
    ላነቆራኝ ያቆራኘን፤
    ባንድ ዘመን ተገናኘን።

    መዝሙሬን እንደሃዘን ሙሾ፣ አላዘበኩኝ በእንባ፤
    ደስታዬን ከደስታህ ላይሰምር፣ ወስጥህ ሰርጾ ልይገባ፤
    የርቅ እጄን ብዘረጋ፣ ደስታህ ላያስፈግገኝ።
    ምን አዚም ከኔ ጣድህ፣
    ምኑ አዚም ከአንተ አዞረኝ።

     

    ከፍካት ናፋቂዎች ይተወሰደ
    በደሉ ዋቅጀራ

  • ቡና በኮረንቲ ከደበነ

    ቡና በኮረንቲ ከደበነ፤
    ባንድ ፍንጀል ከወሰነ፤
    ምኑን ቡና ሆነ!?
    ቡና ይሏችኅል ከተቆላ፤
    እስከ ሶስተኛ የሚፈላ!!!!

    አጀቦት ሲኒ_’ረከቦት _’ጀበና፤
    ወይራ -እጣን -በጊርጊራ ፤
    እንጂ ምኑን ተባለ ቡና!?

    ፉት ሲሉ ካንዱ ሰም ጋር፤
    ካልገባበት አንድ ስካር፤
    ጭልጥ – ከናስሩ ምክር፤
    ካለማጉ – ከሰው ትዳር፤
    ቡና ያኔነው የ’ሚያምርው።

    ፈንድሻ ቄጠማ ተነስንሶ፤
    እንደ ቁርስ -ሃሜት ነክሶ፤
    ካላቆየ ፍቅር ከሶ፤
    ምኑ ቡና ውግ አፍርሶ!!!

    ያሽሙር እጣን ካልተመመ፤
    ቁርሾ አቡክቶ ካልተመመ፤
    ቀናው ነገር ካልጠመመ፤
    በመን ወጉ ቡና ጣመ።

    ያቡና አተላው ሲፈስ፤
    ካልበተነ በጣብ ድግስ፤
    አኮራርፎ ካልመሸገልን–
    ሸንጎው ለነገ ካልተቀጠርን፤
    ቡና አይባለም ይሆናል ቡን።

    ስዩም ተፈራ
    ከሶስቱ እንባዎች ያተወሰደ

“A great song should lift your heart, warm the soul, and make you feel good.”

― Colbie Caillat

Say Hello

If you have an interesting project, or just have some ideas, reach out to us. We’re available.

at info@addisherald.com

Follow Us

Stay up to date on upcoming events, and random posting.